ከዓሊይ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: «አንድ ነፍሱን ገንዘብ ከፍሎ ነፃ ለማውጣት ከአለቃው ጋር የተዋዋለ ባሪያ ወደርሱ መጣና እንዲህ አለው: "እኔ ነፍሴን ከፍዬ ነፃ የማወጣበት ገንዘብ ስላቃተኝ አግዘኝ።" ዐሊይም እንዲህ አለ: "በአንተ ላይ የሲር ተራራን የሚያህል እዳ ቢኖርብህ እንኳ አላህ እንዲከፍልልህ የሚያደርግን የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ያስተማሩኝን ቃላቶች ላስተምርህን?" እንዲህ ብለዋል: ‹እንዲህ በል: አልላሁመክፊኒ ቢሐላሊከ ዐን ሐራሚክ፤ ወአግኒኒ ቢፈድሊከ ዓመን ሲዋክ›"» ትርጉሙም "አላህ ሆይ! በሐላልህ ከሐራምህ ጠብቀኝ፤ በችሮታህም ከአንተ ውጪ ካሉ አብቃቃኝ።" ማለት ነው። ሐሰን ነው። - ቲርሚዚ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

አንድ ከአለቃው ጋር ነፍሱን ለመግዛትና ነፃ ሊያወጣት ተስማምቶ የተፃፃፈ ነገር ግን ገንዘብ የሌለው ባሪያ ወደ አማኞች አዛዥ ዐሊይ ቢን አቢ ጧሊብ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - መጣና እንዲህ አለ: "እኔ ያለብኝን ገንዘብ መክፈል አቅቶኛልና ገንዘቡን በመክፈል ላይ ወይም መፍትሄ የሚሆነኝን በማስተማርና በመጠቆም ላይ አግዘኝ።" የአማኞች አዛዥም እንዲህ አለው: "ጦይእ አካባቢ ውስጥ የሚገኘው የሲር ተራራን የሚያህል እዳ ቢኖርብህ እንኳ አላህ እዳህን ለሚገባው አካል በመክፈል ከመዋረድ እንድትድን የሚያደርግን የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ያስተማሩኝን ቃላቶች ላስተምርህን?" ቀጥሎ እንዲህ አለው: "እንዲህ በል (አልላሁመ ክፊኒ) አላህ ሆይ አርቀኝ፣ አዙረኝ (ቢሐላሊከ) በሐላልህ ተብቃቅቼ (ዐንሐራሚክ) ክልክልህ ላይ ከመውደቅ (ወአግኒኒ) አብቃቃኝ (ቢፈድሊከ) በቸርነትህ (ዐመንሲዋክ) ከአንተ ውጪ ካሉ ፍጡራን።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ለጉዳያችን የእውቀትና የዲን ባለቤቶችን ሀሳባቸውን መጠየቅና ማማከር እንደሚገባ እንረዳለን።
  • የእውቀት ባለቤቶችና ወደ አላህ የሚጣሩ ዱዓቶች ምክራቸውን ለሚሰሙ ሰዎች በሚያጋጥማቸው ችግሮች መፍትሄ መጠቆምና ማቅናት ይገባቸዋል።
  • ነፍሱን ነፃ ለማውጣት የተፃፃፈን ባሪያ በማገዝ ላይ መነሳሳቱን ተመልክተናል።
  • ይህን ዱዓ በመማርና አላህን በዚህ ዱዓ በመጠየቅ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • ሐላል የሆነ ሪዝቅ ቢያንስ እንኳ ከብዙ የሐራም ገንዘብ የተሻለ ነው።
  • ከፍጡራን በአላህ መብቃቃት እንደሚገባ እንረዳለን።
  • ለጠያቂ የምትሰጠው የሌለህ ጊዜ መልካም መልስ በመመለስ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።