ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ ለነርሱ እንዲህ እንደሚል ተናገሩ: እንድጨምርላችሁ የምትፈልጉት አንዳች ነገር አለን? ሁሉም የጀነት ሰዎችም እንዲህ ይላሉ: ፊታችንን አላበራኸውምን? ጀነት አስገብተህስ ከእሳት አላዳንከንምን? አላህም ግርዶሹን አስወግዶ ይገልጠዋል። የፊቱ ግርዶሽም ብርሃን ነው። ወደ ጌታቸው ዐዘ ወጀል ከመመልከት የበለጠ ተወዳጅ ነገርም አይሰጣቸውም።