explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለሰው ልጅ ጀነትም ይሁን ጀሀነም በእግሩ ላይ እንዳለው የጫማው ማሰሪያ ቅርብ መሆናቸውን ተናገሩ። ምክንያቱም (ሳያስበው) አሏህን የሚያስደስት የሆነን መልካም ስራ ይሰራና በዛ ሰበብ ጀነት ይገባል። ወይም መጥፎ ስራ ይሰራና ጀሀነም ለመግባት ሰበብ ይሆንበታል።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ትንሽ ቢሆንም መልካም ስራ ላይ መበርታትና ትንሽ ቢሆንም ከክፋት መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
  • ሙስሊም በህይወቱ በራሱ ሁኔታ ሳይሸወድ ሁሌም በተስፋና በስጋት መካከል ሊሆን እና እውነት ላይ እንዲያፀናውም ጥራት የተገባው አሏህን ሊማፀን የግድ እንደሚገባው እንረዳለን።