ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለሽንትም ይሁን ለሰገራ መፀዳዳት የፈለገ ሰው ወደ ካዕባ አቅጣጫ ዞሮም ይሁን ለካዕባ ጀርባን ሰጥቶ መፀዳዳቱን ከለከሉ። ቂብላው እንደ መዲና ነዋሪዎች ከሆነ ማድረግ ያለበት ወደ ምስራቅ ወይም ምዕራብ አቅጣጫ ዘንበል ማለት ነው። ቀጥሎ አቡ አዩብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ወደ ሻም የገቡ ጊዜ ወደ ካዕባ አቅጣጫ የተገነባ ለመፀዳጃነት የተዘጋጀ መፀዳጃ ቤት እንዳገኙ፤ በአካላቸውም ከቂብላ ዘንበል እንደሚሉና ከዚህም ጋር ግን አላህን ምህረት እንደሚጠይቁ ተናገረ።