ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ባል ሚስቱን ወደ መበደል፣ ወደ መተውና ችላ ወደማለት የሚያደርስ የሆነ ጥላቻን ከመጥላት ከለከሉ። የሰው ልጅ በጉድለት ላይ የተፈጠረ ነው። በሚስቱ ላይ መጥፎ ባህሪዋን ቢጠላ እንኳ ሌላ መልካም ባህሪን እርሷ ላይ ያገኛል። ከርሱ ጋር የሚስማማውን መልካም ባህሪ ይውደድላትና የማይወድላትን መጥፎ ባህሪ ደግሞ ይታገስ። ይህም እንዲታገስ የሚያደርገውና ወደመለያየት የሚያደርስ ጥላቻን ከመጥላት የሚታደግ ነው።