explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንዲት ሴት የጋብቻዋን ውል ለማሰር ሀላፊነት በሚወስድ ወሊይ ካልሆነ በስተቀር ጋብቻ መፈፀም እንደማይበቃላት ገለፁ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የወሊይ መኖር ጋብቻው ትክክለኛ እንዲሆን መስፈርት ነው። ያለ ወሊይ ወይም ሴቲቱ ራሷን ብትድር ጋብቻው አይበቃም።
  • ወሊይ የሚሆነው ወደ ሴቷ እጅግ ቅርብ ዘመድ የሆነ ወንድ ነው። ከርሱ የቀረበ ወሊይ እያለ ሩቅ የሆነ ወሊይ እሷን ማጋባት አይችልም።
  • ወሊይ ለመሆን የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይገባዋል: - አቅመ አዳምና የአይምሮ ጤነኛ (ሙከለፍ) መሆን፣ ወንድ መሆን፣ የጋብቻን ጥቅም የሚያውቅ አስተዋይ መሆኑ (ቂላቂል አለመሆን) ፣ ወሊዩና ተጋቢዋ ተመሳሳይ እምነት መከተላቸው ነው። እነዚህን ባህሪያቶች ያልተላበሰ የጋብቻን ውል በማሰር ረገድ ለወሊይነት የተገባ አይደለም።