ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሙስሊም ወንጀለኛ ወንጀሉን በፉከራና በብልግና ይፋ የሚያወጣ ካልሆነ በቀር የአላህን ይቅርታና ምህረት የማግኘት ተስፋ እንዳለው ገለፁ። ወንጀሉን ይፋ የሚያደርግ ግን ይቅርታ አይገባውም። ምሽት ላይ ወንጀል ይሰራል ከዚያም አላህ ሸሽጎለት አንግቶ ሳለ ለሌላ ሰው ትናንት የሆነች ወንጀልን እንደሰራ ይናገራል። ጌታው ሸሽጎለት አድሮ ሳለ የአላህን ግርዶሽ የገለጠ ሆኖ ያነጋል።