ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንድ ሰው በግራ እጁ ሲበላ ተመለከቱትና በቀኝ እጁ እንዲበላ አዘዙት። ሰውዬውም በኩራትና በውሸት በቀኝ እጁ መብላት እንደማይችል መለሰላቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በቀኝ እጁ መመገብ አሏህ እንዳያስችለው በርሱ ላይ ዱዓ አደረጉበት። ቀኝ እጁን ሽባ በማድረግ አላህ የነቢዩን ዱዓ ተቀበለ። ከዚህ በኋላም ምግብ ወይም መጠጥ ወደ አፉ ማንሳት አልቻለም።