explain-icon

ትንታኔ

አንድ ባሪያ ጌታውን በቸረውና ባጣቀመው ፀጋዎቹ ምክንያት ማመስገኑ የአላህ ውዴታን ከሚያገኝባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ ምግብ በልቶም "አልሐምዱሊላህ" ማለት ፤ የሚጠጣም ጠጥቶ "አልሐምዱሊላህ" ማለት እንደሚገባው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ገለፁ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አላህ ሲሳይን ችሮን በምስጋናችን መደሰቱ የርሱን ችሮታ እንረዳለን።
  • የአላህ ውዴታ ከመብላትና መጠጣት በኋላ ማመስገንን በመሰለ ትንሽ ምክንያት እንኳ እንደሚገኝ እንረዳለን።
  • ከምግብና መጠጥ ስነስርአቶች መካከል ከበሉና ከጠጡ በኋላ አላህን ማመስገን አንዱ ነው።