ከኢብኑ ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "አንዳችሁ የበላ ጊዜ በቀኙ ይብላ። የጠጣም ጊዜ በቀኙ ይጠጣ። ሰይጣን የሚበላውም በግራው፤ የሚጠጣውም በግራው ነውና።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንድ ሙስሊም ሲበላም ሆነ ሲጠጣ በቀኝ እጁ እንዲሆን አዘዙ። በግራው ከመብላትና ከመጠጣትም ከለከሉ። ይህም ሰይጣን የሚበላውም ሆነ የሚጠጣው በግራው ስለሆነ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በግራ በመብላት ወይም በመጠጣት ከሰይጣን ጋር ከመመሳሰል መከልከሉን እንረዳለን።