ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሰው ልጅ አንድ ስፍራ ላይ በሚያርፍበት ጊዜ የሚፈራቸውን ሁሉ አስፈሪ ነገሮች የሚከላከልበትን ጠቃሚ መጠበቂያና መጠጊያ ለኡመታቸው እየጠቆሙ ነው። ይህም ጉዞም ላይ ይሁን ሊዝናናም ይሁን ወይም ከዛ ውጪ ባረፈበት ስፍራ ላይ ከሚገኝ ፍጡራን ሁሉ ክፋት በትሩፋቱ፣ በበረከቱና በጥቅሙ የተሟላ በሆነውና ከሁሉም ነውርና ጉድለት የፀዳ በሆነው የአላህ ቃል ከተጠበቀና ከተጠጋ በዛ ስፍራ እስካለ ድረስ ከሁሉም ጎጂ ነገሮች ደህንነቱ ይጠበቃል።