ፋጢማ ቢንት ሑበይሽ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና): "እኔ የሚፈሰኝ ደም ከወር አበባ ጊዜዬም ውጪ መፍሰሱ አልቋረጥ አለ። ታዲያ የዚህ ደም ብይን እንደ ወር አበባ ደም ብይን ነውን? ሶላትንስ ልተውን?" በማለት ጠየቀች። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሏት: "ይህ በማህፀን ውስጥ የሚገኝ ደም ስር በመቆረጡ ሳቢያ የሚመጣ የበሽታ ደም እንጂ የወር አበባ ደም አይደለም። በበሽታ ደም ከመታመምሽ በፊት በወርሃዊ ልምድሽ የወር አበባን ታይበት የነበርሽበትን የጊዜ መጠን ልክ ሲመጣ ሶላት፣ ፆምና ሌሎችንም የወር አበባ ላይ ያለች ሴት በወር አበባ ወቅት የምትከለከላቸውን ነገሮች ተይ! የወር አበባ ቀናትሽ መጠን በተጠናቀቀ ጊዜ ከወር አበባ ነፅተሻልና የደሙን ስፍራ እጠቢ ከዚያም ሐደሥሽን (ከሶላት የከለከለሽን) ለማስወገድ ሰውነትሽን ሙሉ ትጥበት ታጥበሽ ከዚያም ስገጂ።" አሏት።