ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በጃሂሊያ ዘመን በምፅዋት፣ ነፃ በማውጣትና ዝምድና በመቀጠል የምፈፅማቸው አምልኮዎች ነበሩ በእነሱ እመነዳለውን?" አልኳቸው። ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለው መለሱለት፦ "ካሳለፍከው መልካም ተግባር ጋር ነው የሰለምከው።" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ካፊር የሰለመ ጊዜ ከመስለሙ በፊት በጃሂሊያ ዘመን ይሠራቸው በነበሩት እንደ ሰደቃ፣ ባሪያን ነፃ ማውጣትና ዝምድና መቀጠል የመሰሉ መልካም ሥራዎች እንደሚመነዳ አብራሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ካፊር በዱንያ ለሠራቸው መልካም ሥራዎች በዛው ክህደት ላይ ከሞተ በአኺራ አይመነዳበትም።