ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለት ቀብሮች በኩል አለፉና እንዲህ አሉ፦ የነዚህ ሁለት ቀብር ባለቤቶች እየተቀጡ ነው። አላህ ዘንድ ትልቅ ወንጀል ቢሆንም በናንተ እይታ ግን ትልቅ በሆነ ወንጀል አይደለም የሚቀጡት። አንደኛው: በሚፀዳዳ ወቅት ሰውነቱንና ልብሱን ከሽንት መጠበቅን ትኩረት አይሰጠውም ነበር። ሌላኛው ደግሞ በሰዎች መካከል ነገር በማመላለስ ይዞር ነበር። በሰዎች መካከል መጎዳዳትን፣ ልዩነትን ማምጣትና ሀሜትን አስቦ የሌላን ሰው ነገር ያዋስድ ነበር።