explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መቃብሮች ላይ ከመቀመጥ ከለከሉ። ልክ እንደዚሁ ቀብሩ ወደ ሰጋጁ ቂብላ አቅጣጫ በሆነ ጊዜ ወደ መቃብሮች ዞሮ ከመስገድም ከለከሉ። ይህም የተከለከለው ወደ ሺርክ ከሚያዳርሱ አንዱ ስለሆነ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በሐዲሥ እንደተረጋገጠው የጀናዛ ሶላት ካልሆነ በቀር በመቃብር ስፍራ ወይም በመቃብሮች መካከል ወይም ወደ መቃብር ዙሮ መስገድ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  • ወደ መቃብር መስገድ የተከለከለው የሺርክን መዳረሻዎች ለመዝጋት ነው።
  • ኢስላም በመቃብር ወሰን ማለፍንም መቃብር ማዋረድንም ከልክሏል። በእስልምና ወሰን ማለፍም ማሳነስም የለምና።
  • ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "የሙትን አጥንት መስበር በህይወት እንደመስበር ነው።" ስላሉ የሙስሊም ክብር ከሞተ በኋላም ዘላቂ ነው።