ሰዕድ ቢን ሂሻም ቢን ዓሚር እናታችን ዓኢሻህ ዘንድ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- የገባ ወቅት እንዲህ አለ: "የሙእሚኖች እናት ሆይ! ስለአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር ንገሪኝ! እሷም 'ቁርአን አትቀራምን?' አለችኝ። እኔም 'እንዴታ!' አልኩኝ። እሷም ' የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ስነምግባር ቁርአን ነበር።' አለችኝ።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ረጅሙ የሐዲሥ ጥቅል ውስጥ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

የአማኞች እናት የሆነችው ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- ስለነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር ተጠየቀች። ጠያቂውን ሁሉንም ምሉዕ ባህሪያት ወደ ሰበሰበው ወደ ተከበረው ቁርአን በመመለስ ጠቅላይ በሆነ ንግግር መለሰችለት። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቁርአናዊውን ስነምግባር የተላበሱ ፤ ቁርአን ያዘዘውን ይፈፅሙ፣ ቁርአን የከለከለውን ደግሞ ይርቁ እንደነበር፤ የሳቸው ስነምግባር በቁርአን መስራት ፣ ድንበሩ ላይ መቆም፣ የቁርአንን አዳብ መላበስ ፣ ምሳሌዎቹንና ታሪኮቹን ማስተንተን ነበር ብላ መለሰችለት።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ነቢዩ ቁርአናዊ ስነምግባር በመላበሳቸው ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አርአያ በማድረግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር መሞገሱ። የሳቸው ስነምግባር ከወሕይ ምንጭ የተቀዳ ነውና።
  • ቁርአን ለሁሉም የተከበሩ ስነምግባሮች ምንጭ መሆኑን እንረዳለን።
  • ስነምግባር በኢስላም ሁሉንም የሃይማኖቱን ክፍሎች ያጠቃልላል፤ ይህም ትእዛዛትን በመፈፀምና ክልከላውን በመራቅ ነው።