explain-icon

ትንታኔ

አንድ ሙስሊም ለአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያለው ውዴታ ለእናቱ ፣ ለአባቱ ፣ ለወንድ ልጁ፣ ለሴት ልጁና ለሰዎችም ባጠቃላይ ካለው ውዴታ እስኪያስቀድም ድረስ ኢማኑ ምሉዕ አይሆንም በማለት የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ። ይህ ውዴታም እሳቸውን መታዘዝን፣ መርዳትንና እሳቸውን ማመፅ መተውን ያስፈርዳል።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • መልክተኛውን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መውደድና ከሁሉም ፍጡራን ውዴታ ማስቀደም ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
  • የአላህን መልክተኛ ሱና መርዳትና በዚህ መንገድ ላይም ገንዘብና ነፍስን መለገስ ከተሟላ ውዴታ ምልክቶች መካከል አንዱ ነው።
  • መልክተኛውን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መውደድ ባዘዙት ነገር መታዘዝን ፣ በተናገሩት ማመንን፣ ከከለከሉትና ካስጠነቀቁት ነገሮች መከልከልን፣ እሳቸውን መከተልንና ቢድዓን መተው ያስፈርዳል።
  • ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከጥመት መንገድ (ወደ ቀናው) ለመመራታችን ፣ ከእሳት ለመዳናችን፣ ጀነትን ለመጎናፀፋችን ምክንያት ስለሆኑ የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሀቅ ከሁሉም ሰዎች ሀቅ የበለጠና የገዘፈ ነው።