ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - መስጂዳቸው ውስጥ ከባልደረቦቻቸው ጋር ነበሩ። አንድ ባላገር ከገጠር መጣና የመስጂዱ ጎን ዘንድ ተቀምጦ መሽናት ጀመረ። ሶሓቦችም "አተ አቁም! ተው!" በማለት አስጠነቀቁት። ነቢዩም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - "ተዉት! ሽንቱን አታቋርጡት።" አሉ። እስኪያጠናቅቅም ድረስ ተዉት። ከዚያም ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጠርተው እንዲህ አሉት: መስጂዶች ለሽንትና ለቆሻሻ አይነቶች አይበጁም። መስጂድ የሚበጀው አላህን ለማውሳት፣ ለሶላት፣ ቁርአንን ለመቅራትና ለመሳሰሉት ነው። ቀጥለው ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - አንድን ሶሓባ በውሃ የተሞላ ባልዲ ይዞ እንዲመጣ አዘዙና በቀላሉ ሽንቱ ላይ ደፉበት።