ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዱዓን በአላህ መሻት ላይ እንኳ ቢሆን በነገሮች ማንጠልጠልን ከለከሉ። ምክንያቱም አላህ ካልሻ በቀር እንደማይምር የታወቀና የተረጋገጠ ጉዳይ ነው። ስለዚህም የአላህን መሻት መስፈርት ማድረግ ትርጉም አልባ ነው የሚሆነው። መሻት መስፈርት ሊደረግ የሚችለው በመገደድና በተለያዩ አላህ ራሱን ከርሱ ባጠራባቸው ምክንያቶች ያለፍላጎቱ ሊሰራ ይችላል ለሚባል ሲሆን ነው። ይህንንም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በሐዲሡ መጨረሻ ላይ እርሱ አስገዳጅ የለውም በማለት ገልፀውታል። እንዲሁም ከፈለግክ እስኪባል ድረስ አንድም አላህ የሚሰጠው የሚተልቅበት ነገር የለም። አንድም ነገር የሚሳነውም የለም የሚተልቅበትም የለም። ከፈለግክ በሚለው ቃል ዱዓውን ማንጠልጠሉ ከምህረቱ መብቃቃቱን የሚያሳይም ነው። አንድ ሰው "ልትሰጠኝ ከፈለግክ ስጠኝ።" ቢል ይህንን ቃል ወይ መብቃቃት ላይ ሆኖ ነው የሚናገረው ወይም ደግሞ ሊሰጠው ከማይችል ጋር ነው የሚናገረው። ተቸግሮና ያንን ነገር እየፈለገ ሊሰጠው ከሚችል ጋር ግን ጥያቄውን ቁርጥ ማድረግ ነው ያለበት። ድሃና ከጃይ ሰው የሚጠይቀውን አጠያየቅ ነው የሚጠይቀው። አላህ የተሟላ የተብቃቃ ስለሆነና በሁሉም ነገር ላይም ቻይ ስለሆነ ወደ አላህ ተጠግቶ ነው የሚጠይቀው።