ጀሪር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ወንድ ልጅ ባዳ ሴትን ሳያስበው በድንገት በማየቱ ጉዳይ ጠየቀ። ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዳወቀ ፊቱን ወደሌላ አቅጣጫ ማዞር ግዴታው መሆኑን አሳሰቡት። ይህን ካደረገም ወንጀል እንደማይኖርበት ተናገሩ።