ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አድናቆታዊ በሆነ መልኩ በአማኝ ጉዳይና ሁኔታ ይገረማሉ። ይህም የአማኝ ሁኔታዎች ባጠቃላይ መልካም በመሆናቸው ነው። ይህም ለአማኝ እንጂ ለሌላ አይሆንም። አማኝ የሆነ ሰው ደስታ በሚያጋጥመው ጊዜ በርሱ ላይ አላህን ያመሰግናል። በማመስገኑም ምንዳን ያገኛል። ጉዳት ሲያጋጥመው ደግሞ ይታገሳልም አላህ ዘንድ ምንዳ አገኝበታለሁ ብሎም ያስባል። በትእግሰቱም ምንዳን ያገኛል። ስለዚህ እርሱ በሁሉም ሁኔታዎቹ በምንዳ ላይ ነው።