ሰሐቦች (አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና) በአላህ መንገድ መታገልንና ጠላቶችን መጋደልን እጅግ በላጭ ከሆኑ ተግባራቶች መካከል እንደሆነ አድርገው ይመለከቱ ነበር። ዓኢሻም (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሴቶችም ጂሃድ ማድረግ ሊፈቀድላቸው ዘንድ ጠየቀች። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለሴቶች እጅግ በላጭ የሆነውን ጂሀድ ጠቆሟቸው: እርሱም ቁርኣንና ሐዲሥን የገጠመውና ከወንጀልና ከይዩልኝ የፀዳው ተቀባይነት ያለውን ሐጅ ነው።