ከሑዘይፋ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለቱ ሱጁዶች መካከል 'ረቢጝፊርሊ ረቢጝፊርሊ' 'ጌታዬ ሆይ! ማረኝ! ጌታዬ ሆይ! ማረኝ!' ይሉ ነበር።" ሶሒሕ ነው። - አቡዳውድ፣ ነሳኢ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሁለቱ ሱጁዶች መካከል በሚቀመጡ ጊዜ "ረቢጝፊርሊ ረቢጝፊርሊ" "ጌታዬ ሆይ! ማረኝ! ጌታዬ ሆይ! ማረኝ!" ይሉ ነበር። ይደጋግሟትም ነበር። "ረቢጝፊርሊ" ማለት አንድ ባሪያ ከጌታው ወንጀሎቹን እንዲምረውና ነውሮቹን እንዲሸሽግለት መፈለጉ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በግዴታም ሆነ ሱና ሶላት ውስጥ በሁለቱ ሱጁዶች መካከል ይህንን ዱዓ ማድረግ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
  • "ረቢጝፊርሊ" "ጌታዬ ሆይ! ማረኝ" የሚለውን ዚክር መደጋገም እንደሚወደድ እንረዳለን። ግዴታው ግን አንድ ጊዜ ማለት ነው።