ከአቢ ዐብስ ዐብዱራሕማን ቢን ጀብር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "በአላህ መንገድ ሲታገሉ አቧራ የለበሱ እግሮችን እሳት ልትነካቸው አትችልም።" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአላህ መንገድ እየታገለ እግሮቹን አቧራ የነካው ሰው እሳት እንደማትነካው አበሰሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በአላህ መንገድ የሚታገል ሰው ከእሳት እንደዳነ መበሰሩን እንረዳለን።
  • አቧራው ሰውነትን ባጠቃላይ የሚያዳርስ ከመሆኑም ጋር እግር ተለይቶ የተወሳበት ምክንያት በዛ ዘመን የነበሩት አብዛኛዎቹ ሙጃሂዶች እግረኞች ስለነበሩና በማንኛውም ሁኔታ እግርን አቧራ መንካቱ የማይቀር ስለሆነ ነው።
  • ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «አቧራ እግርን መንካቱ ብቻ እሳትን እርም የሚያደርግላት ከሆነ የለፋ፣ አቅሙን የሰጠና በሙሉ ችሎታው የታገለ ሰውስ እንዴት ሊመነዳ ይሆን?»