explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ቀብራቸውን በማላቅና የሱጁድ አቅጣጫውን ወደዛው በማድረግ ሰዎች ቀብራቸውን እንደሚያመልኩት ጣኦት እንዳያደርግባቸው አምላካቸውን ተማፀኑ፤ ከዚያም የነቢያቶችን መቃብር የአምልኮ ስፍራ አድርገው በሚይዙ ላይ የአሏህ እርግማን እንደሰፈነባቸውና ከእዝነቱም እንዳባረራቸው አሳወቁ። ምክንያቱም መቃብሩን የአምልኮ ስፍራ አድርጎ መያዝ የቀብሩን ባለቤት እንዲመለክ ለማድረግና በተቀበረበት አካል ዙርያ አጉል እምነት ለማሳደር መዳረሻ ነውና።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የነብያትና የጻድቃን ሰዎች መቃብርን በተመለከተ ሸሪዓው ያስቀመጠውን ገደብ ማለፉ ከአላህ ሌላ የሚመለኩ ጣኦት እንዲሆኑ ስለሚያደርጋቸው ወደ ሽርክ (ሽርክ) ከሚመሩ መንገዶች መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
  • ቀብሩ ውስጥ የተቀበረው አካል ወደ አሏህ ምንም አይነት ቅርበት ቢኖረውም ቀብሩን ለማላቅም ይሁን በመቃብሩ አሏህን ለማምለክ ማለም አይፈቀድም።
  • መስገጃን መቃብር ላይ መገንባት የተከለከለ ነው።
  • ሟቹ ላይ ሶላተል ጀናዛ ያልሰገደበት ሰው ቀብሩ ዘንድ መስገድ ይፈቀድለታል። ከዛ ውጪ ግን መስጂድ ባይገነቡ እንኳ መቃብር ዘንድ መስገድ የተከለከለ መሆኑን እንረዳለን።