ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በምሽት ውስጥ የበቀራህ ምእራፍ የመጨረሻዎቹን ሁለት አንቀፆች የቀራ ሰው አላህ መጥፎና ጎጂ ከሆኑ ነገሮች እንደሚበቃው ተናገሩ። ለሌሊት ሶላት ከመቆም ይበቁታል ማለት ነውም ተብሏል። ሌሎች ውዳሴዎችን ከማለት ይበቁታል ማለት ነውም ተብሏል። ለሌሊት ሶላት የሚቀራ ዝቅተኛው በቂ የቁርአን አንቀፆች ናቸውም ተብሏል። ከዚህም ውጪ ተብሏል። ምንአልባት ሁሉም ከላይ የተጠቀሱትን ትርጓሜዎችን ቃሉ ስለሚሰበስባቸው ሁሉም ትክክለኛ ትርጓሜ ሊሆኑ ይችላሉ።