explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በምሽት ውስጥ የበቀራህ ምእራፍ የመጨረሻዎቹን ሁለት አንቀፆች የቀራ ሰው አላህ መጥፎና ጎጂ ከሆኑ ነገሮች እንደሚበቃው ተናገሩ። ለሌሊት ሶላት ከመቆም ይበቁታል ማለት ነውም ተብሏል። ሌሎች ውዳሴዎችን ከማለት ይበቁታል ማለት ነውም ተብሏል። ለሌሊት ሶላት የሚቀራ ዝቅተኛው በቂ የቁርአን አንቀፆች ናቸውም ተብሏል። ከዚህም ውጪ ተብሏል። ምንአልባት ሁሉም ከላይ የተጠቀሱትን ትርጓሜዎችን ቃሉ ስለሚሰበስባቸው ሁሉም ትክክለኛ ትርጓሜ ሊሆኑ ይችላሉ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የሱረቱል በቀራህ የመጨረሻ አንቀፆች ትሩፋት መገለፁ። እሱም { አመነ አርረሱሉ …} ከሚለው የአላህ ንግግር እስከምእራፉ መጨረሻ ያለውን ነው።
  • የበቀራህ ምእራፍ መጨረሻዎች ምሽት ላይ ለሚቀራቸው ሰው ከጉዳት፣ ከመጥፎና ከሰይጣን ይከላከላሉ።
  • ምሽት ፀሃይ በመግባት ጀምሮ ጎህ በመውጣቱ ይጠናቀቃል።