ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በርሳቸው ላይ ንጋት የገባ ጊዜ (ይህም ጎህ ከመውጣቱ ጋር የቀኑ መጀመሪያ የሆነ ጊዜ ነው።) እንዲህ ይሉ ነበር: (አላህ ሆይ! በአንተ አነጋን) በጥበቃህ ተከልለን፣ በፀጋህ ተሸፍነን፣ አንተን በማውሳት ተጠምደን፣ በስምህ ታግዘን፣ በመግጠምህ ተከበን፣ በብልሃትህና በሀይልህ ተንቀሳቃሽ ሆነን አነጋን ማለት ነው። (በአንተ አመሸን፣ በአንተ ህያው እንሆናለን፣ በአንተም እንሞታለን።) ይህ ማለት ምሽት ላይ ከማድረግ ጋር ቀደም ተብሎ እንደተብራራው እንዲህ ይላል: አላህ ሆይ ባንተ አምሽተናል፣ ህያው አድራጊ በሆነው ስምህ ህያው እንሆናለን። ህይወትን የሚነጥቅ በሚለው ስምህ እንሞታለን። (መቀስቀስም ወዳንተ ነው።) መቀስቀስ ከሞት በኋላ ነው፤ መለያየት ከመሰብሰብ በኋላ ነው። በሁሉም ወቅቶች ሁኔታችን በዚህ ሁኔታ ይቀጥላል። በተቀሩትም ሁኔታዎቼ ከአላህ አልላቀቅምም አልተወውምም። ከዐስር በኋላ ምሽት የገባ ጊዜም (አላህ ሆይ! በአንተ አመሸሁ፣ በአንተም አነጋሁ፣ በአንተም ህያው እንሆናለን፣ በአንተም እንሞታለን፣ መመለስም ወደ አንተ ነው።) ይሉ ነበር። በዱንያም መመለሻዬ፣ በመጨረሻም መመለሻዬ ወደ አንተ ነው። ህያው የምታደርገኝም አንተው ነህ፤ የምትገድለኝም አንተው ነህ። ማለት ነው።