ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አራጣ በሚገባባቸው ስድስቱ የገንዘብ አይነቶች ዙሪያ ትክክለኛውን የመገበያያ መንገድ ገለፁ። እነርሱም: ወርቅ፣ ብር፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ተምርና ጨው (አሞሌ) ናቸው። ተመሳሳይ የሆኑ ገንዘቦችን በተመሳሳይ ገንዘብ መለዋወጥ ከሆነ ወርቅን በወርቅ፣ ብርን በብር ... ለመሳሰሉት የግድ ሁለት መስፈርቶች መሟላት አለባቸው: የመጀመሪያው: እንደወርቅና ብር በሚዛን የሚመዘኑ ከሆነ ሚዛናቸው ተመሳሳይ መሆን አለበት። ወይም እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ተምርና ጨው በስፍር የሚሰፈሩ ከሆኑ ደሞ የስፍር ልካቸው ተመሳሳይ መሆን አለበት። ሁለተኛው: ሻጩ ገንዘቡን ገዢ ሸቀጡን መውሰዳቸው ነው። ይህም የሚሆነው ንግዱ በተፈፀመበት ቦታ ነው። መለዋወጡ ወርቅን በብር መለዋወጥ፣ ተምርን በስንዴ መለዋወጥ ይመስል የገንዘብ አይነቶቹ በተለያዩበት ከሆነ ግን አንድ መስፈርት ብቻ ከተሟላ በቂ ነው። እርሱም ሻጩ ገንዘቡን ገዢውም ሸቀጡን በግብይይቱ ስፍራ ላይ መውሰዳቸው ነው። ይህ ካልሆነ ግብይቱ የተበላሸ ነው። ክልክል የሆነው አራጣ ላይም ወድቀዋል። በዚህ ወንጀል ላይም ሻጩም ሆነ ገዢው እኩል ናቸው።