በንግግሩ ወይም በተግባሩ እውነትና መልካም ወዳለበት መንገድ ሰዎችን የመራ፣ የጠቆመና የቀሰቀሰ ሰው የተከታዩን አምሳያ ምንዳ እንደሚያገኝና ይህም ከተከታዩ ምንዳ አንዳችም ሳይቀነስ እንደሆነ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ። በንግግር ወይም በተግባር ወንጀልና ኃጢአት ወይም የማይፈቀድ ነገር ወዳለበት የጥመትና የክፋት መንገድ ሰዎችን የጠቆመ ሰውም የተከታዩን አምሳያ ወንጀልና ኃጢአት ይኖርበታል። ይህም ከነርሱ ወንጀል አንዳችም ሳይቀነስ ነው።