ከአቡ ሙሐመድ ዐብደላህ ቢን ዐምር ቢን አልዓስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦ "አንዳችሁ ዝንባሌው ይዤ የመጣሁትን እስከሚከተል ድረስ አላመነም።" قال النووي: حديث صحيح - رويناه في كتاب الحجة بإسناد صحيح
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አንድ ሰው ውዴታው መልክተኛው -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይዘውት የመጡትን ትእዛዛትን፣ ክልከላዎችንና ሌሎችንም እስከሚከተል ድረስ፤ እርሳቸው ያዘዙትን እስኪወድና የከለከሉትንም እስኪጠላ ድረስ ኢማኑ የተሟላ አማኝ አይሆንም ብለው አብራሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ይህ ሐዲሥ ለሸሪዓ እጅ ለመስጠትና ታዛዥ ለመሆን መርህ የሆነ ሐዲሥ ነው።
  • የአይምሮውን ወይም የባህሉን ፍርድ መልክተኛው -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይዘውት ከመጡት መመርያ የሚያስቀድም ሰው ከርሱ ላይ ኢማን ውድቅ መደረጉ ለሁሉም ሰው ማስጠንቀቂያ ነው።
  • ሐዲሡ ላይ «ይዤው ለመጣሁት» ማለታቸው በሁሉም ነገር ሸሪዓን ማስዳኘት ግዴታ መሆኑን ያስረዳናል።
  • ኢማን በአምልኮ ይጨምራል በወንጀል ደግሞ ይቀንሳል።