ከሂሻም ቢን ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንደተላለፈው: ሂሻም በሻም ውስጥ በሚገኙ ዐረብ ባልሆኑ ገበሬዎች ፀሐይ ላይ እንዲቆሙ በተደረጉ ሰዎች በኩል አለፈ። እርሱም: "ምን ሆነው ነው?" አለ። ሰዎችም "ግብር ባለመክፈላቸው ለቅጣት እዚሁ ታስረው ነው።" ብለው መለሱለት። ሂሻምም «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ሲሉ እንደሰማው እመሰክራለሁ: "እነዚያን በዱንያ ውስጥ ሰዎችን የሚቀጡን ሰዎች አላህ ይቀጣቸዋል።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ሂሻም ቢን ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- ዐረብ ባልሆኑ ገበሬዎች በኩል ሲያልፍ ከፀሐይ ሐሩር በታች እንዲቆሙ ተደርገው ተመለከተ። ስለ ሁኔታቸውም ጠየቀ። ይህ የተደረገባቸው ግብር መክፈል እየቻሉ ባለመክፈላቸው እንደሆነም ተነገረው። ሂሻምም -አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና- ከአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ሲሉ እንደሰማው እመሰክራለሁ አለ: አላህ ያለ አግባብ በግፍ በዱንያ ውስጥ ሌሎችን የሚቀጡ ሰዎችን ይቀጣቸዋል።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ጂዝያ (ግብር) ማለት: የመጽሐፍ ሰዎች ሆነው አቅመ አዳም በደረሱና ሀብታም በሆኑ ወንዶች ላይ በሙስሊሞች አገር ስለሚኖሩና ስለተሰጣቸው ከለላ እንዲከፍሉ የሚመደብባቸው ገንዘብ ነው።
  • ያለ ሸሪዓዊ አስገዳጅ ምክንያት ከሃዲን እንኳን ቢሆን ሰዎችን መቅጣት ክልክል እንደሆነ እንረዳለን።
  • በዳዮች ለበደላቸው እንደተዛተባቸው እንረዳለን።
  • የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ባልደረቦች በመልካም ማዘዝና ከመጥፎ መከልከልን እንዴት አጥብቀው ይተገብሩ እንደነበር እንረዳለን።
  • ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የሚተረጎመው ያለ አግባብ በመቅጣት ነው። እንደ ቂሷስ (የገደለን መግደል)፣ (ሑዱድ) የሸሪዓዊ መቀጮዎችን ማስፈፀም፣ ስርዓት ለማስያዝ መቅጣትና የመሳሰሉት አግባብ የሆኑ ቅጣቶችን መቅጣት ሐዲሡ ውስጥ አይካተትም።"