ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - በሠሙዶች መኖሪያ በኩል ሲያልፉ ወደዚህ መንደር የሚገባ ሰው እነርሱ ላይ የደረሰውን በማስተንተን እያለቀሰ ካልሆነ በቀር ነፍሳቸውን ወደበደሉ ሰዎች መንደር ከመግባት ወይም ከመምጣት ከለከሉ። ይህም እነርሱን እንዳገኛቸው አይነት ቅጣት እንዳያገኘው ስለሚያሰጋ ነው። ቀጥለው እንስሳቸውን በጩኸት አስነስተው አልፈው እስኪሄዱ ድረስ ፈጥነው ተጓዙ።