ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአማኞች በስተቀር ማንም ጀነት እንደማይገባ፤ ከፊሉ ከፊሉን እስኪወድ ድረስም ኢማን እንደማይሞላና የሙስሊሙ ማህበረሰብ ሁኔታም እነደማይስተካከል ገለፁ። ከዚያም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በርሱ አማካኝነት ውዴታ የሚዳረስበትን በላጭ ነገር ጠቆሙ። እርሱም: በሙስሊሞች መካከል አላህ ለባሮቹ ሰላምታ መለዋወጫ ያደረገውን ሰላምታን ማሰራጨት ነው።