ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ጣዕረ ሞት ላይ ሳሉ ለኡመታቸው አብዝተው ይመክሩት የነበረው ምክር: "ሶላትን አጥብቃችሁ ያዙ፤ በመስገዱም ላይ ተጠባበቁ፤ ከሶላትም አትዘናጉ። ልክ እንደዚሁ በእጆቻችሁ ስር ያሉትን ባሪያዎችንም መብት ጠብቁ። ለባሮቻችሁ በጎ ስሩ።" የሚል ነበር። ይህንን ምክር ሲሉም ጉሮሯቸውን እስኪተናነቃቸው ድረስ ከመደጋገም አልተወገዱም። ምላሳቸውም ቃሉን ለማውጣት ይሳነው ነበር።