የአማኞች እናት ዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ለይለተል ቀደርን በመፈለግ በመጨረሻዎቹ የረመዳን አስር ቀናቶች ኢዕቲካፍ በማድረግ እንደሚያሳልፉ ይህንንም አላህ ሩሓቸውን እስከወሰደበት ጊዜ ድረስ እንደቀጠሉበትና ከርሳቸው በኋላም ሚስቶቻቸው (ረዺየሏሁ ዐንሁነ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ኢዕቲካፍ ማድረጉን እንደቀጠሉበት ተናገረች።