የአማኞች እናት ከሆነችው ከዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው፦ «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት የወጡ ጊዜ "ጉፍራነክ" ይሉ ነበር።» (ትርጉሙም "ምህረትህን እለምንሃለሁ" ማለት ነው።) ሶሒሕ ነው። - አቡዳውድ፣ ቲርሚዚ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት ተፀዳድተው ሲወጡ አላህ ሆይ ምህረትህን እጠይቃለሁ ይሉ ነበር።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ከመፀዳጃ ስፍራ ሲወጣ "ጉፍራነክ" ማለት እንደሚወደድ እንረዳለን።
  • ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሁሉም ሁኔታቸው ጌታቸውን ምህረት እንደሚጠይቁ እንረዳለን።
  • ከመፀዳጃ ቤት ሲወጣ ምህረትን የሚጠየቅበት ምክንያት አላህን ለብዙ ፀጋዎቹ ከማመስገን ስላጓደልን ሲሆን ከነዛም ፀጋዎቹ መካከል የሚያውከንን ነገር እንዲወጣ ማቅለሉ አንዱ ነው። በምፀዳዳበት ወቅት አንተን ከማውሳት ስለተጠመድኩ ምህረትህን እጠይቅሃለሁ ይባላልም ብለዋል።