ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - በፋንዲያ ወይም በአጥንት ኢስቲንጃእ (ከተፀዳዱ በኋላ ከማዳረቅ) ከለከሉ። "ሁለቱም አያፀዱም።" ብለዋል።» ሶሒሕ ነው። - ዳረቁጥኒይ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከሸና ወይም ሰገራውን ከተጠቀመ በኋላ በእንስሶች አጥንት ወይም በፍጋቸውና በፋንዲያቸው ከማደራረቅ ከለከሉ። እንዲህም አሉ: እርሷ ነጃሳን አታስወግድምም አታፀዳምም።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አንዳንድ የመፀዳዳትና የኢስቲንጃእ ስነስርዓት መገለፁ።
  • በፋንዲያ (ፍግ) ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጃሳ ስለሆነ ነው ወይም የጂን እንስሶች ቀለብ ስለሆነ ነው።
  • በአጥንት ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጂስ ነው። ወይም ለጂኖች ምግብ ስለሆነ ነው።