ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሙስሊሞችን ከከሃዲያን ለመጠበቅ ስራውን ለአላህ አጥርቶ በሙስሊሞችና በከሃዲዎች መካከል ያለ ኬላ ላይ ጥበቃ እያደረጉ አንድ ቀንም ማሳለፍ ከዱንያና ውስጧ ካለው እንደሚበልጥ፤ አንድ ባሪያ ጀነት ውስጥ በአላህ መንገድ የሚታገልበት አለንጋ ያህል ቦታ ማግኘቱ ከዱንያና ውስጧ ካለው እንደሚበልጥ፤ ከቀኑ መጀመሪያ እስከ ዝሁር ድረስ ባለው ወይም ከዝሁር ወቅት እስከ ምሽት ድረስ ባለው ጊዜ በአላህ መንገድ አንድ ጊዜ የመጓዝ ምንዳና አጅር ከዱንያና ውስጧ ካለው እንደሚበልጥ ተናገሩ።