ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአንድ ልብስ የሰገደ ሰው ሁለት ትከሻዎቹን (ከአንገቱ እስከ ማጅራቱ ያለውን) አንዳች መሸፈኛ በነርሱ ላይ ሳያደርግ ራቁት አድርጎ መስገዱን ከለከሉ። ሁለቱ ትከሻዎች ሀፍረተ ገላ ባይሆኑም እንኳ ሀፍረተ ገላ ሲሸፈኑ አብሮ ለመሸፈን የተመቹ ናቸውና። በሶላት ውስጥ አላህ ፊት ሲቆምም አላህን ለማላቅና ለማክበር የቀረበ ነው።