ከኢብኑ ዐባስ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለአሸጅ ዐብዲል ቀይስ እንዲህ አሉ: "አንተ ውስጥ ሁለት አላህ የሚወዳቸው ነገሮች አሉ። እነርሱም አስተዋይነትና መረጋጋት ናቸው።"» ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - የዐብዱል ቀይስ የሚባል ጎሳ መሪ ለሆነው ለሙንዚር ቢን ዓኢዝ አሸጅ -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና- እንዲህ አሉት: አንተ ውስጥ አላህ የሚወዳቸው ሁለት ባህሪያት አሉ። እነርሱም: አስተዋይነት፣ ማረጋገጥ፣ እርጋታና አለመቸኮል ናቸው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አስተዋይነትንና እርጋታን በመላበስ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • ነገሮችን በማረጋገጥና የሚያስከትሉትን ነገር በመመልከት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • አስተዋይነትና እርጋታ ምስጉን ከሆኑ ባህሪያቶች መካከል ነው።
  • ሰዎች አላህ በተፈጥሮ ላጎናፀፋቸው ምስጉን ስነምግባር አላህን ማመስገን እንደሚገባቸው እንረዳለን።
  • አሸጅ ማለት ፊት ላይ ወይም ጭንቅላት ላይ ወይም ግንባር ላይ የቆሰለ ማለት ነው።