ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሙስሊም የሆነ ሰው ለሙስሊም ወንድሙ ከሩቅ ‐ ዱዓ የሚደረግለት ሰው በሌለበት ‐ የሚያደርገው ዱዓ ተቀባይነት እንዳለው ተናገሩ። ይህም የኢኽላስ ጥግ የደረሰ ዱዓ ስለሆነ ነው። ዱዓ አድራጊው ጭንቅላት ዘንድም የተወከለ መልአክ እንዳለና ለወንድሙ መልካም ነገርን ዱዓ ባደረገ ቁጥር ለዚህ ጉዳይ የተወከለው መልአክ "አሚን ላንተም ዱዓ ያደረግከውን አምሳያ ይስጥህ።" እንደሚልም ተናገሩ።