ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መልካም ስራ ከመፈፀም የሚከለክሉና የሚያቅቡ ፈተናና ማምታቻዎች መጥተው መልካም ስራ መስራት ከባድ ከመሆኑ በፊት አማኞች ወደ መልካም ስራ እንዲቻኮሉና እንዲያበዙ አነሳሱ። ይህም ፈተና እንደ ሌሊት ቁራጭ ድቅድቅ ጨለማ በመሆኑ እውነቱ ከሀሰት ጋር ተደበላልቆ ለሰዎች እውነትን ከውሸት መለየት የሚከብድበት ፈተና ነው። ከፈተናዋ መክበድ የተነሳ ሰውዬው አማኝ ሆኖ አንግቶ ከሀዲ ሆኖ እስኪያመሽ፤ አማኝ ሆኖ አምሽቶ ከሀዲ ሆኖ እስኪያነጋና ጠፊ በሆነው አለማዊ ጥቅም ሃይማኖቱን እስኪተው ድረስ ሰዎች ይዋልላሉ።