explain-icon

ትንታኔ

አላህ በአንድ አማኝ ባሪያው ላይ መልካምን የፈለገ ጊዜ በነፍሳቸው፤ በገንዘባቸውና በቤተሰቦቻቸው እንደሚፈትናቸው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ተናገሩ። ይህም አንድ አማኝ በሱ ምክንያት ወደ አላህ በዱዓእ መጠጋት፣ የወንጀል መማርና የደረጃ ከፍ ማለትን ስለሚያገኝ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አማኝ የሆነ ሰው ለተለያዩ የመከራ አይነቶች የተጋለጠ ነው።
  • ፈተና የአንድ አማኝን ደረጃ ከፍ ከማድረጉ፣ ማዕረጉን ከመስቀሉና ወንጀሉን ከማስማሩ አኳያ አላህ ለባሪያው ላለው ውዴታ ምልክት ሊሆን ይችላል።
  • በመከራዎች ላይ ትእግስት በማድረግና ባለመበሳጨት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።