ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በግማትና ቀፋፊነት በአህያ ጥንብ ላይ እንደተሰባበሱ ሰዎች አምሳያ ሆነው የሚነሱ እንጂ አንድ ስፍራ ላይ ተቀምጠው ከዚያም በዛ ስፍራ አላህን ሳያወሱበት የሚነሱ ሰዎች የሉም። ይህም አላህን ከማውሳት በወሬ ስለተጠመዱ ነው። የትንሳኤ ቀንም በዚህ አቀማመጣቸው ሰበብ በነርሱ ላይ ቁጭት፣ ጉድለትና ፀፀት እንደማይለቃቸው ተናገሩ።