ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንድ ሙስሊም በአላህ ላይ ያለውን እሳቤ አሳምሮ ካልሆነ በቀር እንዳይሞት አነሳሱ። ይህም ጣእረ ሞት ላይ የሆነ ጊዜ አላህ እንደሚያዝንለትና ይቅር እንደሚለው በማሰብ ተስፈኝነቱን በማመዘን ነው። በሸሪዓ አላህን መፍራት የተፈለገው ስራችንን እንድናሳምር ስለሚረዳን ነው። ይህ ያለበት ሁኔታ ደግሞ የስራ ሁኔታ አይደለምና በዚህ ሁኔታ ላይ የሚፈለገው ተስፈኝነትን ማመዘን ነው።