ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሙስሊም የሆነ ሰው ትንሽ ብትሆን እንኳ አንዳች የሚናዘዘው ሐቅ ወይም ገንዘብ ኖሮ ኑዛዜው እርሱ ዘንድ የተፃፈች ካልሆነች በቀር ሶስት ቀናትን ማደር እንደማይገባው ተናገሩ። ዐብደላህ ቢን ዑመርም ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ: " የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይህንን ሲናገሩ ከሰማው ጀምሮ ኑዛዜዬ እኔ ዘንድ የተፃፈች ሆና እንጂ አንድም ምሽት አድሬ አላውቅም።"