ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: አዛን አድራጊውን የሰማ ጊዜ እንዲህ ያለ ሰው: "አሽሃዱ አን ላኢላሃ ኢለሏሁ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ" ማለትም: ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለና ከርሱ ውጪ የሚመለኩ ሁሉ ከንቱ እንደሆኑ አረጋግጣለሁ፣ አውቃለሁ፣ እናገራለሁ። "ወአነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ" ማለትም: እርሳቸው ባሪያ ናቸውና አይመለኩም፣ መልክተኛ ናቸውና አይስተባበሉም። "ረዲቱ ቢላሂ ረበን" ማለትም: በአላህ ጌትነት፣ ተመላኪነትና በስሞቹና በባህሪያቱ ወድጃለሁ። ማለት ነው። "ወቢሙሐመደን ረሱላ" ማለትም ረሱል በተላኩበት ነገር ሁሉና ባደረሱን ነገር ወድጃለሁ። ማለት ነው። "በእስልምናም" ማለትም: ትእዛዛትም ሆኑ ክልከላዎች በሁሉም የኢስላም ህግጋት "ዲና" ማለትም በማመንና በመመራት ወድጃለሁ። ማለት ነው። "ወንጀሉ ይማራል።" ማለትም ትናንሽ ወንጀሎቹን ይማሩለታል።