ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሙዓዝን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እጅ ያዙና ለርሱ እንዲህ አሉት: በአላህ እምልልሃለሁ እኔ እወድሃለሁ። ሙዓዝ ሆይ! በየሁሉም ሶላት መጨረሻ ላይ ይህን ማለት እንዳትተው አደራ እልሃለሁ። "አሏሁመ አዒኒ ዐላ ዚክሪከ" (አላህ ሆይ! አንተን በማውሳት አግዘኝ) ወደ አምልኮ የሚያቃርበኝ በሆነ ንግግርና ተግባር ሁሉ አግዘኝ። "ወሹክሪከ" ፀጋን በማግኘትና መከራን በማስወገድም (አንተን ለማመስገን) አግዘኝ። ለአላህ ስራን በማጥራትና ነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመከተል (አምልኮህን በማሳመርም) አግዘኝ።