ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ጂብሪል ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘንድ ተቀምጦ ሳለ ከበላዩ ድምፅ ሰማና ራሱን ቀና አደረገ። እንዲህም አለ: "ይህ ዛሬ የተከፈተ የሰማይ በር ነው። ከዛሬ በቀርም ተከፍቶ አያውቅም።" ከተከፈተው በርም መልአክ ወረደ። ጂብሪልም እንዲህ አለ: "ይህ ወደ ምድር የወረደ መልአክ ነው። ከዛሬ በቀርም በጭራሽ ወርዶ አያውቅም" መልአኩም ሰላምታን አቀረበና እንዲህ አለ: "ከአንተ በፊት ማንም ያልተሰጠው በሆነ ለአንተ ብቻ በተሰጠህ ሁለት ብርሃኖች አበስርሃለሁ። (እነርሱም) የመጽሐፉ መክፈቻ (ፋቲሓ) እና የበቀራ ምዕራፍ መጨረሻዎቹ ናቸው። ከነርሱም አንድም ፊደል አታነብም የሚሰጥህ ቢሆን እንጂ።"» ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

መልአኩ ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘንድ ተቀምጦ ሳለ ከሰማይ በር ሲከፈት እንደሚያሰማው አይነት ድምፅ ሰማ። ጂብሪልም ራሱንና አይኑን ወደ ሰማይ ቀና አደረገ። ቀጥሎ ለነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና -ይህ የሰማይ በር ዛሬ እንደተከፈተና ከዚህ ቀን በፊትም በፍፁም ተከፍቶ እንደማያውቅ ነገራቸው። ከሰማይም ወደ ምድር ከመልአኮች መካከል ከዛሬ በቀር ወርዶ የማያውቅ አንድ መልአክ ወረደ። መልአኩም ለነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ሰላምታን አቀረበና እንዲህ አላቸው: ከአንተ በፊት ለማንም ነቢይ ባልተሰጡና ለአንተ ብቻ በተሰጠህ ሁለቱ ብርሃኖች አበስርሃለሁ። እነርሱም: የፋቲሓ ምዕራፍና የበቀራ ምዕራፍ የመጨረሻዎቹ ሁለት አንቀጾች ናቸው። አስከትሎም መልአኩ እንዲህ አለ: አንድም ሰው ከነርሱ አንድ ፊደል እንኳ ብትሆን ካነበበ አላህ በውስጧ ያለውን መልካም ነገር፣ ተማፅኖና ፍላጎት ይሰጠዋል።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የፋቲሓ ምዕራፍና የበቀራ ምዕራፍ መጨረሻዎች ያላቸውን ደረጃና እነርሱን በመቅራትና ውስጣቸው ባለው መልዕክት በመስራት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • ሰማይ መለኮታዊ ትእዛዛት የሚወርዱበት በሮች እንዳለውና የሰማይ በርም ያለ አላህ ትእዛዝ እንደማይከፈት እንረዳለን።
  • ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጌታቸው ዘንድ ያላቸው ክብር ተገልጿል። ይኸውም ከርሳቸው በፊት ማንንም ነቢይ ባላከበረበት እርሳቸውን ማክበሩና እነዚህን ሁለት ብርሃኖች መስጠቱ ነው።
  • ወደ አላህ ከመጣሪያ መንገዶች መካከል በመልካም ማበሰር አንዱ ነው።