ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "መላእክት ውሻ እና ቃጭል ካላቸው መንገደኞች ጋር አብረው (አይጎዳኙም) አይሄዱም።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በጉዞ ወቅት በመካከላቸው ውሻ ካለ ወይም በእንስሶች ላይ የሚንጠለጠለውና ሲንቀሳቀስ ድምፅ የሚያወጣው ቃጭል ካለ መላእክት ከነርሱ ጋር በወዳጅነት እንደማይጎዳኙ ተናገሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ከአደን ውሻና ከጥበቃ ውሻ በቀር ውሻ መያዝና መጎዳኘት መከልከሉን እንረዳለን።
  • ከመጎዳኘት የሚቆጠቡት መላእክቶች የእዝነት መላእክት ናቸው። የሰውን ስራ የሚቆጣጠሩት መላእክት ግን ባሮችን ቤታቸውም ውስጥ ሆኑ ጉዞ ላይ አይለዩዋቸውም።
  • ቃጭል መከልከሉን እንረዳለን። ምክንያቱም እርሱ ከሰይጣን መዝሙሮች መካከል አንዱ ነውና። ቃጭል በውስጡ የክርስቲያኖች ደወል ጋር መመሳሰልን ያቀፈ ነው።
  • አንድ ሙስሊም መላእክትን የሚያርቅ ከሆነ ነገር ሁሉ በመራቅ ላይ ሊጥር እንደሚገባ እንረዳለን።